Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

Sunday 12 May 2024

ታላቋ አርበኛ ወይዘሪት ሆይ ከበደች ስዩምን የሚዘክር መርሃ ግብር ነገ ይካሄዳል

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

አርበኛ ወይዘሪት ሆይ ከበደች ስዩምን የሚዘክር መርሃ ግብር በነገው ዕለት ቅዳሜ ግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም በወመዘክር አዳራሽ ታላላቆች በታደሙበት ይከናወናል፡፡ በተጨማሪም የአርበኛዋን አንጸባራቂ ገድል የሚያሳይ  አጭር ድራማም ለታዳሚው ይቀርባል፡፡

በታሪካችን ሂደት ሴቶች  ያላቸውን አስተዋፅኦ የሚዘክር ልዩ የፓናል ውይይት ከኪነ-ጥበባዊ ዝግጅቶች ጋር ታጅቦ እንደሚቀርብም አዘጋጆቹ ተናግረዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ ዶ/ር ዘካሪያስ አምደብርሀን፣ ሴቶችን ከኢትዮጵያ ታሪክ አንጻር የሚያስቃኝ ጥናታዊ ጽሁፍ የሚያቀርቡ ሲሆን፤ ወይዘሮ ዮዲት አምሀ አበራ ደግሞ  የሴቶችን የስነልቦና ጥንካሬና እንዴት ይበረታታሉ? በሚለው ላይ አተኩረው ጥናታዊ መረጃ ያቀርባሉ ተብሏል፡፡




 የህግ ባለሙያዋ ወይዘሮ ማሪያ ሙኒር ደግሞ  ሴቶች ከወንድሞቻቸው ጎን በመቆም  እንዴት የለውጥ ሀዋርያ ይሆናሉ? በሚለው ላይ ሀሳብ ያጋራሉ፡፡ የጅማ ዩኒቨርሲቲ የአንደኛ አመት ተማሪ  ኤልዳና ዮሀንስ በበኩሉ፤ አዲሱ ትውልድ ምን ይጠበቅበታል? በሚለው ላይ ጠንካራ ሀሳብ  እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል፡፡ 

በነገው ዕለት የሚታወሱትና የሚዘከሩት አርበኛ ወይዘሪት ሆይ  ከበደች ስዩም፤ የዛሬ 83 አመት በተደረገው የኢትዮጵያና የጣሊያን ጦርነት ላይ  ከፍተኛ የድል መንፈስ የነበራቸውና በጦር ሜዳው ላይም በጀግንነታቸው የተወደሱ ነበሩ፡፡

No comments:

Biruh Media

በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና ላይ በቀን 1/9/2016 ዓ.ሞ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ዝና ከባድ ብ ምክንያት በበልግ ስብልና ሌሎች ንብረ...