Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

Monday 1 February 2021

በኢትዮጵያ የግንባታ ስራዎች ባልተገባ መንገድ በተወሰኑ ስራ ተቋራጮች እጅ እየገባ መሆኑን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር አስታወቀ።

በመሰረተ ልማት ስራዎች ዙሪያ እየተፈጠሩ ያሉ ተግዳሮቶች በተገቢው ሁኔታ ስራ መስራት እንዳልችል አድርጎኛል ሲል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር አስታወቀ፡፡ ማህበሩ በስራ ሂደት እየገጠሙኝ ነው ባላቸው የስራ መስኮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ማህበሩ በተለያዩ የግንባታ ዘርፎች መንግስታዊ ግዥ ፈጻሚ መስሪያ ቤቶች በኩል ከሚታዩ የኢፍትሃዊ የግንባታ ግዥ አፈጻጸም ጀምሮ እየተከናወኑ ያሉ ግንባታዎች በተወሰኑ ድርጅቶች ብቻ እንዲገነቡ የመፍቀድ ሁኔታዎች መበራከታቸው ግንባታዎችን ከማጓተቱ ባለፈ ለተለያዩ ብልሹ አሰራሮች እንዲጋለጥ እንዳደረገው ማህበሩ አስታውቋል፡፡

 
 May be an image of road

No comments:

Biruh Media

በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና ላይ በቀን 1/9/2016 ዓ.ሞ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ዝና ከባድ ብ ምክንያት በበልግ ስብልና ሌሎች ንብረ...