Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

Thursday 25 July 2019

የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የከተማ አስተዳደሩ ቅድመ ዝግጅቶን አድርጌያለው አለ



ሐምሌ 22 ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የከተማ አስተዳደሩ ባደረጋቸው ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ የከንቲባ ፅ/ቤት ፕሬስ ሴክረቴሪያት ወ/ት ፌቨን ተሾመ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡






ወ/ት ፌቨን በመግለጫቸው ፦

✿ የቦታ ልየታን ጨምሮ ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን፤

✿ በከተማዋ ባሉ 116 ወረዳዎች ወጣቶችን በማሳተፍ 2.8 ሚሊየን ጉድጓድ ቁፋሮ መደረጉን ፤

✿ በዕለቱ 400 በላይ የመትከያ ሳይቶች መዘጋጀታቸውን ፤

✿ በከተማዋ ያሉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የሚሳተፍበት ቦታ ተዘጋጅቷል ፤

✿ በዕለቱ 100ሺ የሚሆኑ ወጣቶች ዝግጅቱን ለማስተባበር መዘጋጀታቸውን ፤

✿ በዕለቱ የሚሰሩ ስራዎችን የሚመራ ግብረ ሃይል መቋቋሙን በመግለጫቸው ጠቅሰዋል፡፡

ስለዚህ በአራዳ ክ/ከተማ ፣ ልደታ ክ/ከተማ ፣ ቂርቆስ ክ/ከተማ እና አዲስ ከተማ ክ/ከተማ የመትከያ ሰፋፊ ቦታ የሌላቸው ወረዳዎች ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቅዳሜ ጠዋት ጀምሮ በወረዳቸው በመገኘት ችግኞችን በመውሰድ በጊቢያቸው እና በ20/50 ራድየስ መትከል ይችላሉ፡፡

በማስፋፍያ አከባቢ የሚኖሩ የከተማዋ ነዋሪዎች በየአከባቢዎቻቸው በተዘጋጁ የመትከያ ጣቢያዎች በመገኘት መትከል ይችላሉ፡፡

በዕለቱ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞች በሙሉ የችግኝ ተከላ ላይ ስለሚሳተፉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ለአገልግሎት ዝግ ይሆናሉ፡፡

የከተማው ነዋሪ ለከተማው ያለውን ፍቅር እና በጎ አመለካከት ችግኝ በመትከል በተግባር እንዲገልፅ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

No comments:

Biruh Media

በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና ላይ በቀን 1/9/2016 ዓ.ሞ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ዝና ከባድ ብ ምክንያት በበልግ ስብልና ሌሎች ንብረ...