Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

Friday 26 July 2019

የጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የፍርድ ሂደት

ፌደራል ፖሊስ ቀጠሮ የጠየቀበትን ምክንያት እንዲያቀርብ ትናንት ለዛሬ ቀጠሮ የጠየቀዉ የፊደራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ፍትሃብሔር ችሎት የጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ         አካልን ነፃ የማዉጣት ክስ ዉድቅ አደረገ።
የጋዜጠኛዉ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ጉዳዩን ለበላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ እንደሚሉ                   አስታዉቀዋል።

Thursday 25 July 2019

ችሎቱ



በሙስና ወንጀል የተከሰሱትን የአቶ በረከት ስምዖን፤ የአቶ ታደሰ ካሳን እና በአባሪ ተባባሪነት የተጠረጠሩትን የቀድሞ የብአዴን-ኢሕአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ጉዳይ የሚዳኘዉ ፍርድ ቤት፣ አቃቤ ሕግ በተከሳሾች ላይ ያቀረባቸዉን የሰነድ ማስረጃዎች በአማርኛ ቋንቋ ተርጎሞ እንዲያቀርብ አዘዘ።


ዛሬ ባሕርዳር ያስቻለዉ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንዳለዉ አቃቤ ሕግ ካቀረበዉ ከ1000 ገፅ የሚበልጥ የሰነድ ማስረጃ መካከል አብዛኛዉ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተፃፈ ነዉ። የክልሉ የሥራ ቋንቋ አማርኛ በመሆኑ አቃቤ ሕግ ለምስክርነት ያቀረበዉን ሰነድ ሙሉ በሙሉ በአማርኛ አስተርጎሞ ለመስከረም 22፣ 2012 እንዲያቀርብ ፍርድ ቤቱ አዝዟል። ተከሳሾች ደግሞ መስከረም 30፣ 2012 እንዲቀርቡ ወስኗል። ተከሳሾች ግን፣ አቃቤ ሕግ ሰነዶቹን ሳይተረጉም ያቀረበዉ «ሆን ብሎ» ክሱ የሚታይበትን ጊዜ ለማራዘም ነዉ በማለት ቅሬታቸዉን ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል። የባሕርዳሩ ወኪላችን ዓለምነዉ መኮንን እንደጠቀሰዉ አቃቤ ሕግ ማስረጃዎቹን እስካሁን በነበረዉ ጊዜ አስተርጎሞ ማቅረብ ይገባዉ እንደነበር ለችሎ
ቱ አስተያየት ሰጥተዋል።

የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የከተማ አስተዳደሩ ቅድመ ዝግጅቶን አድርጌያለው አለ



ሐምሌ 22 ለሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የከተማ አስተዳደሩ ባደረጋቸው ቅድመ ዝግጅቶች ዙሪያ የከንቲባ ፅ/ቤት ፕሬስ ሴክረቴሪያት ወ/ት ፌቨን ተሾመ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡






ወ/ት ፌቨን በመግለጫቸው ፦

✿ የቦታ ልየታን ጨምሮ ሌሎች ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን፤

✿ በከተማዋ ባሉ 116 ወረዳዎች ወጣቶችን በማሳተፍ 2.8 ሚሊየን ጉድጓድ ቁፋሮ መደረጉን ፤

✿ በዕለቱ 400 በላይ የመትከያ ሳይቶች መዘጋጀታቸውን ፤

✿ በከተማዋ ያሉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ የሚሳተፍበት ቦታ ተዘጋጅቷል ፤

✿ በዕለቱ 100ሺ የሚሆኑ ወጣቶች ዝግጅቱን ለማስተባበር መዘጋጀታቸውን ፤

✿ በዕለቱ የሚሰሩ ስራዎችን የሚመራ ግብረ ሃይል መቋቋሙን በመግለጫቸው ጠቅሰዋል፡፡

ስለዚህ በአራዳ ክ/ከተማ ፣ ልደታ ክ/ከተማ ፣ ቂርቆስ ክ/ከተማ እና አዲስ ከተማ ክ/ከተማ የመትከያ ሰፋፊ ቦታ የሌላቸው ወረዳዎች ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ከቅዳሜ ጠዋት ጀምሮ በወረዳቸው በመገኘት ችግኞችን በመውሰድ በጊቢያቸው እና በ20/50 ራድየስ መትከል ይችላሉ፡፡

በማስፋፍያ አከባቢ የሚኖሩ የከተማዋ ነዋሪዎች በየአከባቢዎቻቸው በተዘጋጁ የመትከያ ጣቢያዎች በመገኘት መትከል ይችላሉ፡፡

በዕለቱ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞች በሙሉ የችግኝ ተከላ ላይ ስለሚሳተፉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ለአገልግሎት ዝግ ይሆናሉ፡፡

የከተማው ነዋሪ ለከተማው ያለውን ፍቅር እና በጎ አመለካከት ችግኝ በመትከል በተግባር እንዲገልፅ የከተማ አስተዳደሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

የሃዋሳ አስተዳደር፣የሲዳማ እና የሃድያ ዞን ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከሃላፊነት ታገዱ

ደኢህዴን የሃዋሳ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ የሲዳማ እና የሃድያ ዞን ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ከሃላፊነት ማገዱን ይፋ አድርጓል። በሌላ በኩል ንቅናቄው ዛሬ በጀመረው ለ5 ቀናት ይዘልቃል በተባለው ስብሰባ በሃገራዊ እና ክልልላዊ ወቅታዊ የሰላም ጉዳዮች እና በክልል ለመደራጀት በቀረቡ ጥያቄዎች መነሻነት የተዘጋጀው የጥናት ውጤት ላይ ይመክራልም ተብሏል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ደኢህዴን ዛሬ ባወጣው መግለጫ የሃዋሳ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ የሲዳማ እና የሃድያ ዞን ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ከሃላፊነት ማገዱን ይፋ አድርጓል። በሌላ በኩል ንቅናቄው ከከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮቹ ጋር ዛሬ መምከር ጀምሯል።

ለ5 ቀናት ይዘልቃል የተባለው ይኽው ስብሰባ ከሚመክርባቸው ጉዳዮች መካከል ሃገራዊ እና ክልልላዊ ወቅታዊ የሰላም ጉዳዮች እና በክልል ለመደራጀት በቀረቡ ጥያቄዎች መነሻነት የተዘጋጀው የጥናት ውጤት ይገኙበታል።

Biruh Media

በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና ላይ በቀን 1/9/2016 ዓ.ሞ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ዝና ከባድ ብ ምክንያት በበልግ ስብልና ሌሎች ንብረ...