Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

Wednesday 17 February 2021

ታሪፍ ጭማሪ

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ  - በአዲስ አበባ ከተማ ታክሲዎች በነበረው ታሪፍ ላይ ጭማሪ ተደረገ፡፡ 

 #taxi #Price #Ethiopia #biruhmedia #ታክሲ




Saturday 6 February 2021

በቡሬ ከተማ የምግብ ዘይት ማምረቻ ተገነባ

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ - በ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው ፊቤላ እንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ ነገ ይመረቃል ። 

 May be an image of text

ፋብሪካዉ በቀን 1ሺህ 500 ቶን የምግብ ዘይት የሚያመርት ሲሆን፣ ለዘይት ይወጣ ከነበረው 30 በመቶ ወጪውን የሚያስቀር ነዉም ተብሏል ። ባለሃብቱና የቢኬጂ ቦርድ ሊቀመንበሩ አቶ በላይነህ ክንዴ በሰጡት መግለጫ ፍብሪካው ከዘይት ማምረት በተጨማሪ በቀን 200 ቶን ሰሊጥ ማቀነባበር : በቀን 96 ቶን ሳሙና ፣ የአትክልትና ማርጋሪት ማምረቻ፣ የፕላስቲክና ጠርሙስ እንዲሁም የካርቶን ፍብሪካዎችን በውስጡ እንደሚያመርት ተናግረዋል።

የኢትጵያ ንግደ ባንክ ከምስራቅ አፍሪካ ባንኮች መካከል የመጀመሪያውን ደረጃ አገኘ፡፡

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ -  የኢትጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው የአውሮፓውያን 2020 በጀት አመት አፍሪካ ውስጥ ከሚገኙ 100 ባንኮች መካከል የ 17ኛ፣ ከምስራቅ አፍሪካ ደግሞ 1ኛ ደረጃ በመያዝ አመቱን ማጠናቀቁን አፍሪካ ቢዝነስ እና ዘ አፍሪካ ሪፖርት በጥናታቸው ይፋ አደረጉ፡፡
የአፍሪካ ባንኮች በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት በተከሰተው የኢኮኖሚና የንግድ መቀዛቀዝ ሳይበገሩ ከባለፉት 10 ዓመታት የተሻለ የካፒታል መጠን በማስመዝገብ አመቱን አጠናቀዋል፡፡ ባንኮች አማራጭ አገልግሎቶችን በማስተዋወቅና በዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች አማካኝነት ተደራሽነትን ለማስፋት ያደረጉት ጥረት የኮቪድ ተጽዕኖን በመቋቋም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንዳስቻላቸው የጥናት ሪፖርቶቹ አስነብበዋል፡፡ 
 
 
 May be an image of skyscraper, sky and text
 
ጥናቶቹ እንዳመለከቱት አፍሪካ ውስጥ የባንኮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ የመጣ ቢሆንም፣ የባንክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር እና በባንክ የሚንቀሳቀሰው የገንዘብ መጠን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መጥቷል፡፡ እ.ኤ.አ በ2004 ዓ.ም በናይጄሪያ 89 ባንኮች በአገልግሎ ላይ የነበሩ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ 2019 ዓ.ም የባንኮቹ ቁጥር ወደ 27 መውረዱ በጥናቱ ተጠቁሟል፡፡ በኬንያም በተመሳሳይ 10 ባንኮች ሲዋሃዱ 3 ባንኮች ደግሞ ከስራ ውጭ ሆነዋል፡፡
በሌላ በኩል በደቡብ አፍሪካ የሚንቀሳቀሰውና ሙሉ በሙሉ በዲጂታል የባንክ አገልግሎት ላይ የተሰማራው ታይም ባንክ እ.ኤ.አ በየካቲት 2019 ዓ.ም በቀን እስከ 6000 የባንክ ሂሳቦች መክፈት የቻለ ሲሆን፣ በኮቪድ ወረርሽኝ ምክንያት እንቅስቃሴዎች በተገቱበት ወቅት ብቻ ከ400 ሺ በላይ የባንክ ሂሳቦችን በመክፈት ከ613 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ መሰብሰብ መቻሉን አስታውቋል፡፡ ይህም በአፍሪካ ብዙ ያልተነካውን የዲጂታል የባንክ አገልግሎት በመጠቀም ባንኮቹ ወረርሽኙ የደቀነውን አደጋ መቋቋም መቻላቸውንና በገንዘብ ንክኪ ምክንያት ለወረርሽኝ መስፋፋት አመቺ የነበረውን አሰራር ማስቀረት መቻሉን አመላካች ነው፡፡

ዋሻ የከበሩ ድንጋዮች እና አርት ኢግዚቢሽን ተከፈተ።

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ -  ከዛሬ ጥር 29 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም ለሁለት ቀናት መስቀል ፍላወር ዚግዛግ እና ስፖ ለመጀመሪያ ጊዜ በተከፈተው ኢግቢሽን ላይ ሀያ አንድ ነጋዴዎች ተሳታፊዎች ናቸው። የሀገር ውስጥ ሸማቾችን ወደ ገበያው ለመሳብ አላማ ያደረገው ኢግዚቢሽን ላይ ስዕል፣የከበሩ ማዕድናት፣

 No description available.

 የባህል አልባሳት፣የቆዳ ውጤቶች ፣የሀገር ውስጥ ማር፣ስእሎች፣የግእዝ የሰአትና የቀን አቆጣጠር ያላቸው ሰአቶችና ቀለበቶች እንዲሁም የተለያዩ ጌጣጌጦች፣የስጦታ ካርዶች እና ሌሎችም ቀርበውበታል።

Thursday 4 February 2021

🔴 Ethiopia : የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በማህበራዊ ሚድያ ለተጠየቁ ጥያቄዎች መልስ | Ethiopia


via https://youtu.be/Ak70n3tGf8I

የዶ/ር አምባቸው መኮንን ፋውንዴሽን ምስረታ ይፋ ሆነ

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ -  በፋውንዴሽኑ የምስረታ ዝግጅት ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤና አክቲቪስት ታማኝ በየነ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል። በልደታ አካባቢ ለፋውንዴሽኑ የሚሆን የመስሪያ ቤት ቦታም ተበርክቷል ።
ፋውንዴሽኑ ዶክተር አምባቸው በህይወት እያሉ የጀመሯቸውን ሊሰሯቸው የሚችሏቸውን ስራዎች ለማስቀጠል እንደሆነ የዶክተር አምባቸው ልጅ መዓዛ አስታውቃለች። May be an image of Tsgaye Adimasu and text
ፋውንዴሽኑ በትምህርት፣ በጤና እና በአረንጓዴ ልማት ከሚሰራቸው ስራዎች በተጨማሪ እውነትንና ሀቀኝነትን ይዞ የአገርን ልማት የሚያግዝ ማህበረሰብ ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።

ዳንኤል ክብረትን እናወግዛለን ማለትኮ

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ
በእዉቀቱ ስዩም ከፃፈዉ የተወሰደ
ብልፅግና ፓርቲን ለመደገፍ በተካሄደው ሰልፍ ላይ ወዳጄ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሲወገዝ አይቸ ገረመኝ ! ብልጥግናን እንደግፋለን ዳንኤል ክብረትን እናወግዛለን ማለትኮ “ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እንሞታለን በረኛውን ግን እንገድለዋለን “ እንደማለት ነው
#DanielKibret #Ethiopia #biruhmedia#BewketuSeyoum


May be a cartoon of 2 people and text

Wednesday 3 February 2021

2 years ago

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

ህፃን ሚሊዮን አብይ ከነዶክተር ቤተሰብ

ለከንቲባነት አቶ ልደቱ አያሌዉ

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ

አቶ ልደቱ አያሌዉ አያሌዉ በ6ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ለአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ከንቲባነት ሊወዳደሩ ነዉ ።
 
 May be an image of 2 people and text that says 'አቶልደቱአያሌው ለከንቲባነት?? BIRUH MEDIA'

የልዩ ፍላጎት ትምህርት ቤት ግንባታ አስጀመሩ

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ በዲቦራ ፋዉንዴሽን ማእከል የልዩ ፍላጎት ትምህርት ቤት ግንባታ አስጀመሩ
የቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በዲቦራ ፋዉንዴሽን ለሚገነባዉ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ቤት ፕሮጀክት 19 ሚሊዩን ብር የመደበ ሲሆን የፕሮጀክቱ የገንዘብ ምንጭ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ለትምህርት ቤቶች ግንባታ ከሰጡት የመደመር መጽሀፍ ሽያጭ ነዉ፡፡
 
 May be an image of ‎1 person and ‎text that says '‎The Foundation Stone For The First Lady Dibora High School Project Has Been Laid by H.E. Wro. Zinash Tayachew on Feb. 2/2021 ه የልዩፍላጎት ትምህርት ቤት ግንባታ -አስጀመሩ BIRUH MEDIA‎'‎‎

Monday 1 February 2021

ጀኔራል አበባዉ ታደሰ ህንፃዉን ተረከበ

 የጀነራል አበባዉ ህንፃ የሆነዉ አልዋቅ ሆቴል በቀደሙት አመታት ለሼህ አላሙዲን ተሸጦ የነበረ ሲሆን መረጃዎች እንደሚያመላክቱት ለባለቤቱ ጀነራል አበባዉ ተመላሽ ሆኗል ። ህንፃዉን ለባለቤቱ ተመላሽ እንዳደረጉ የገለፀዉ የመረጃ ምንጫችን ሼህ ሙሀመድ አላሙዲንም አልዋቅ ሆቴልን የራስህ ሆቴል ነበር አሁንም በትግስትህና ባለህ ቁርጠኝነትና ሀገርህ በምጥ ሰዓት ስትፈልግህ ለሂወትህ ሳትሰስት አለሁልሽ ብለህ ተገኝተሃልና ቀድሞውኑ ያንተ ነበር አሁንም በስምህ ይጽና የደምና የሂወት ዋጋህንም መልሰህ ውሰድ" በማለት ሆቴሉን መልሰው አስረክበውታል ሲል ጠቅሷል ።

በአዲስ አበባ የእሳት ቃጠሎ

 

ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በምርጫ ዙሪያ ምላሽ ሊሰጡ ነዉ

 በምርጫ ብቻ ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ምርጫ ቦርድን ይጠይቁ በሚል ርእስ የማህበራዊ ሚድያ ተሳትፎ መድረክ በኢትዮጲያ ምርጫ ቦርድ የተዘጋጀ ሲሆን የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ሀሙስ ጥር 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ጠዋት 5 ሰአት ላይ በፌስቡክ ገፅ በቀጥታ ለጠያቂዎቻቸዉ ምላሽ እንደሚሰጡ ምርጫ ቦርዱ በፌስቡክ ገፁ ላይ አስታዉቋል ፡ ማንኛዉም ሰዉ በዚህ የቀጥታ ስርጭት ላይም እንዲይሳተፉ፣ ጥያቄዎቻቸውንም በማህበራዊ ገፁ መልዕክት መሰጫ ላይ ቢልኩለት ዝግጁ መሆኑን አስታዉቋል ።

የምርጫ ቦርዱን ይፋዊ የፌስ ቡክ ገፅ ለማግኘት

በኢትዮጵያ የግንባታ ስራዎች ባልተገባ መንገድ በተወሰኑ ስራ ተቋራጮች እጅ እየገባ መሆኑን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር አስታወቀ።

በመሰረተ ልማት ስራዎች ዙሪያ እየተፈጠሩ ያሉ ተግዳሮቶች በተገቢው ሁኔታ ስራ መስራት እንዳልችል አድርጎኛል ሲል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር አስታወቀ፡፡ ማህበሩ በስራ ሂደት እየገጠሙኝ ነው ባላቸው የስራ መስኮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ማህበሩ በተለያዩ የግንባታ ዘርፎች መንግስታዊ ግዥ ፈጻሚ መስሪያ ቤቶች በኩል ከሚታዩ የኢፍትሃዊ የግንባታ ግዥ አፈጻጸም ጀምሮ እየተከናወኑ ያሉ ግንባታዎች በተወሰኑ ድርጅቶች ብቻ እንዲገነቡ የመፍቀድ ሁኔታዎች መበራከታቸው ግንባታዎችን ከማጓተቱ ባለፈ ለተለያዩ ብልሹ አሰራሮች እንዲጋለጥ እንዳደረገው ማህበሩ አስታውቋል፡፡

 
 May be an image of road

ሁለት ተጨማሪ አካባቢዎች

ዛሬም በሁለት ተጨማሪ አካባቢዎች እሳት ለማስነሳት የተደረገው ሙከራ ከሽፏል።

የጥፋት አላማቸው ያልተሳካላቸው አካላት ሆን ብለው ህብረተሰቡን ለማሸበር እያደረጉት ያለው ተግባር እንደማይሳካ እናሳውቃለን።
ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ ተገቢውን ጥንቃቄ እያደረገ፣ ሳይዘናጋ ነቅቶ አካባቢውን በመከታተል እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መረጃ በመለዋወጥ ያለምንም ስጋት መደበኛ እንቅስቃሴውን ማስቀጠል እንደሚኖርበት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት አስታወቀ

2 years ago

 


ህፃን ሚሊዮን አብይ ከነዶክተር ቤተሰብ
 May be an image of 5 people, people standing and indoor
 May be an image of 5 people, people standing, people sitting and indoor

Biruh Media

በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና

Biruh Media - ብሩህ ሚዲያ በዎላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ዩካራ ቀበሌ ዶንጎ ቀጠና ላይ በቀን 1/9/2016 ዓ.ሞ ከቀኑ 11:00 ጀምሮ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ዝና ከባድ ብ ምክንያት በበልግ ስብልና ሌሎች ንብረ...